ክፍል 101-401

አባል ይሁኑ። ይደጉ። ያገልግሉ። ያጋሩ።

CLASS ምንድን ነው?

ሪክ ዋረን የተፈጠረ፣ የክፍል የደቀመዝሙርነት ፕሮግራም የቤተክርስቲያንዎን ሰዎች በመንፈሳዊ ለማሳደግ የተረጋገጠ መንገድ ነው።

 

  • CLASS ወደ መንፈሳዊ ለውጥ ይመራል — ሰዎችዎ የቃሉ ሰሚ እና አድራጊዎች እንዲሆኑ ያስታጥቃቸዋል።
  • CLASS በስፋት ተፈትኗል - ከ35 ዓመታት በላይ በSaddleback ቤተክርስቲያን እና በሺዎች የሚቆጠሩ አብያተ ክርስቲያናት—በሁሉም መጠን እና ቅርፅ—በዓለም ዙሪያ ተምረውታል።
  • CLASS ሙሉ ለሙሉ ሊበጅ የሚችል ነው — ለአጠቃቀም ቀላል የሆኑ ፋይሎችን እናቀርባለን።

ከጓደኞችዎ ጋር ያጋሩ!
   

የCLASS ኮር በአራት ክፍሎች የተዋቀረ ነው፦

  • 101፦ የቤተክርስቲያናችንን ቤተሰብ ማወቅ
  • 201፦ መንፈሳዊ ብስለቴን ማወቅ
  • 301፦ አገልግሎቴን ማወቅ
  • 401፦ የሕይወቴን ተልዕኮ ማወቅ

የእያንዳንዱ ክፍል ግብዓቶች የአስተማሪ መመሪያና የተሳታፊ መመሪያን ያካትታሉ። የአስተማሪው መመሪያ ከሪክ ዋረን የማስተማር ምክሮችን እና ግልባጮችን ይዟል። የተሳታፊወ መመሪያ ቁልፍ ነጥቦችን፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን እና ማስታወሻዎችን ይዟል።

ከጓደኞችዎ ጋር ያጋሩ!
   

ከእያንዳንዱ ኮርስ ምን እንደሚጠበቅ፡-

ክፍል 101

ይህ ኮርስ የተነደፈው ሰዎች የጥምቀትን አስፈላጊነት እና የቤተክርስቲያን አባልነትን ጨምሮ የክርስትና እምነት መሰረታዊ ነገሮችን እንዲገነዘቡ ለመርዳት ነው። በተለይ ለአዲስ ክርስቲያኖች ወይም ክርስትናን ለመጀመሪያ ጊዜ ለሚመረምሩ ሰዎች ጠቃሚ ሊሆን ይችላል።

ክፍል 201

ይህ ኮርስ በመንፈሳዊ እድገት ላይ የሚያተኩር ሲሆን ጠንካራ የጸሎት ህይወት ለማጎልበት፣ መጽሐፍ ቅዱስን ለመረዳትና ከሌሎች አማኞች ጋር ግንኙነት ለመፍጠር የሚያግዙ መሳሪያዎችን ይሰጣል። እምነታቸውን ለማጠናከር እና ለመንፈሳዊ ጉዟቸው ጠንካራ መሰረት ለመገንባት ለሚፈልጉ ጠቃሚ ሊሆን ይችላል።

ክፍል 301

ይህ ኮርስ የእርስዎን ልዩ ስጦታዎችና ተሰጥኦዎች በማግኘት ብሎም በመጠቀም በቤተክርስቲያንዎ እና በማህበረሰብዎ ውስጥ ሌሎችን ማገልገል ላይ ያተኩራል። በቤተክርስቲያናቸው ውስጥ የበለጠ ለመሳተፍና በሌሎች ህይወት ላይ ተፅዕኖ ለማምጣት ለሚፈልጉ ሊጠቅም ይችላል።

ክፍል 401

ይህ ኮርስ እምነትዎን ለሌሎች በማጋራት እና ሌሎችን ደቀ-መዛሙርት የሚያደርግ ደቀ መዝሙር መሆን ላይ ያተኩራል። ወንጌልን በማካፈል እና ሌሎች በእምነታቸው እንዲያድጉ ለማገዝ የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ለሚፈልጉ ሊጠቅም ይችላል።

ከጓደኞችዎ ጋር ያጋሩ!
   

ቤተ ክርስቲያንዎ የሪክ ዋረንን CLASS ኮርሶችን ስትተገብር እነዚህን ጥቅሞች ያገኛሉ፦

የአባላቶቻችሁን መንፈሳዊ ብስለትን ማጠናከር

እነዚህን ኮርሶች መስጠት የቤተክርስቲያንዎ አባላት በእምነታቸው እንዲያድጉ እና ከእግዚአብሔር ጋር ጥልቅ ግንኙነት እንዲፈጥሩ እድሎችን ይሰጣል። ይህም በመንፈሳዊ ነገር የበሰሉ ጉባኤዎችን የሚያስገኝ ሲሆን በዚህም የሕይወትን አስቸጋሪ ሁኔታዎች ለማለፍ በዙሪያዎ ባለው ዓለም ላይ በጎ ተጽዕኖ ለማሳደር የሚያስችል ብቃት ያለው ጉባኤ ያስገኛል።

አባላትን ለአገልግሎት ማስታጠቅ

በክፍልአባላትን ለአገልግሎት ማስታጠቅ 201 እና ክፍል 301፣ የቤተክርስቲያንዎ አባላት ሌሎችን ለማገልገል ልዩ ስጦታዎቻቸውን እና ክህሎቶቻቸውን ለይተው ያዳብራሉ። ይህም የማህበረሰብዎን ፍላጎቶች ለማሟላት በተሻለ ሁኔታ የበቃ እና ንቁ የሆነ ጉባኤ እንዲኖር ያደርጋል።

ጠንካራ የማህበረሰብ ስሜት መገንባት

CLASSን በትንሽ ቡድን ሲያቀርቡ፣ ቤተ ክርስቲያንዎ በአባላትዎ መካከል ጠንካራ ማህበረሰብን ታሳድጋለች። ይህም ደግሞ ጥልቅ ግንኙነቶችን እና የላቀ የባለቤትነት ስሜትን ያመጣል፣ ይህም የቤተክርስቲያንዎን አጠቃላይ ጤናማነት ለማጠናከር ይረዳል።

አበረታታች የወንጌል ስብከት አገልግሎት

ክፍል 401 አባላትዎ እምነታቸውን በግልፅ እና በሚስብ መንገድ እንዲካፈሉ ያስታጥቃቸዋል። ይህም ሌሎችን ከእግዚአብሔር ጋር ለማገናኘት በትጋት የሚፈልግ የላቀ የወንጌል ጉባኤን ያመጣል።

በማደግ ላይ ያሉ መሪዎች

በክፍል 301 እና ክፍል 401 ቤተ ክርስቲያንዎ በተለያዩ የአገልግሎት ዘርፎች ለማገልገል የበቁ መሪዎችን ታዘጋጃለች። ይህም ወደፊት ቤተክርስቲያንዎን ለመምራት የሚያስችል ብቃት ያለው እና ውጤታማ የአመራር ቡድን ያስገኛል።

ከጓደኞችዎ ጋር ያጋሩ!